በአባላት ላይ በዲሲፕሊን ጉድለት ስለሚወሰዱ እርምጃዎች

ማንኛውም አባል በሚከተሉት ሁኔታዎች ከተግሣጽ ጀምሮ ከአባልነት እስከ ማሰናበት የሚያደርስ እርምጃ ሊወሰድበት ይችላል፤

  1. የፓርቲውን ፕሮግራም፣ መተዳደሪያ ደንብ፣ ውሳኔዎችና መመሪያዎች ያላከበረ ወይም ሌሎች ጥፋቶችን የፈጸመ አባል ወይም ዕጩ አባል ጉዳዩ በዝርዝር ታይቶ እንደ ጥፋቱ ክብደት የዲስፕሊን እርምጃ ይወሰድበታል፤
  2. ማንኛውም አባል የፓርቲውን የአባልነት መዋጮ በተከታታይ ለ6 ወራት አሳማኝ ባልሆነ ምክንያት ካልከፈለ እና ውዝፍ መዋጮውን ለመክፈል ፍቃደኛ ካልሆነ ከአባልነቱ በራሱ ፈቃድ እንደለቀቀ ይቆጠራል፤
  3. ማንኛውም አባል በትክክለኛ መረጃ ላይ ሳይመሠረት አባላትን ከመለመለ ወይም ከአባልነት ካገለለ፣ አባላትን ከወነጀለ በዲስፕሊን ጥፋት ይጠየቃል፤
  4. ማንኛውም አመራር ወይም አባል የሐሰት ሪፖርት መስጠትም ሆነ መጠቀም ክልክል ነው፤
  5. በፓርቲው ውስጥ አንጃነት እና ቡድንተኝነት መፍጠር ወይም ማስፋፋት ክልክል ነው፤
  6. ማንኛውም አባል የሌላ ፖለቲካ ፓርቲ አባል መሆኑ ከተደረሰበት ከፓርቲ አባልነቱ ይሰረዛል፤
  7. ከላይ የተዘረዘሩት እንደተጠበቁ ሆነው በአገሪቱ ህጎች ጥፋት ተብለው የሚቆጠሩ ድርጊቶችን ፈፅሞ የተገኘ መሆኑ ሲረጋገጥ በፓርቲው አሠራርም ተጠያቂ ይሆናል፤

  8. የፓርቲው አባላትና ዕጩ አባላት የሚፈጽሟቸው ጥፋቶች ክብደት እየታየ የሚከተሉት እርምጃዎች ይወሰዳሉ፡-

    ለሙሉ አባል፤

    • ተግሣጽ፤
    • የቃል ማስጠንቀቂያ መስጠት፤
    • የጽሑፍ ማስጠንቀቂያ መስጠት፤
    • ከኃላፊነት ማገድ፤
    • ከኃላፊነት ዝቅ ማድረግ፤
    • ከኃላፊነት ማንሣት፤
    • ከአባልነት ማገድ፤
    • ከአባልነት መሠረዝ።